+251 900 14 14 14/ +251 900 15 15 15

ሎተሪ/LOTTERY

ውድ ኢትዮጵያውያን በዚህ ሰዓት በኢትዮጵያ ሀገራችን በተለያዩ ግጭቶችና በተፈጥሮ አደጋዎች ሳቢያ ከ26 ሚሊያን በላይ ወገናችን፤ የሚበላውና የሚጠጣው አጥቶ በሰቀቀን ተኮራምቶ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም ሕክምና ለማግኘት የጤና ተቋማት ሳይቀር ወድመዋል፡፡ በመሆኑም በመላው ዓለም ላይ የምንኖር ኢትዮያውያን ‹‹የኢትዮጵያን ሕመም ኢትዮጵያውያን ያክሙታል!›› በሚል ኃይለ ቃል፤ የትኛውም የውጪ ድርጅት እርዳታ ሳያስፈልገን የራሳችንን ሕመም በራሳችን ልዩነት ሳይከፋፍለን ተደጋግፈን ማከም እንድንችል፤ሁላችንም ይህን ሽልማት የሚያስገኘውን ሎተሪ በመግዛት የነፍስ በረከት እንድናገኝ በኢትዮጵያዊነት ፍቅርና ክብር ‹‹ኢትዮጵያን እናክማት!›› ሰብአዊ እና በጎ አድራጎት ድርጅት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ለዚህም ባላችሁበት እንደደገፋችሁን ፈጣሪ ይደግፋችሁ፡፡

ለዚህም ‹‹የኢትዮጵያን ሕመም ኢትዮጵያውያን ያክሙታል!›› በሚል ኃይለ ቃል የሚከናወኑ የተለያዩ መርሀ-ግብሮችን በመላው ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተደራሽ በሚሆን መልኩ ከተለያዩ መንግስታዊና የግል ሀገር በቀል ተቋማት እንዲሁም ከመላው ኢትዮጵያውያን ጋር በመተባበር አሰናድቶ ተፈጻሚ ለማድረግ፤ በመላው ዓለም የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያውያን ኑ! ኢትዮጵያን ለማከም ያገረሸባትን ሕመም አስቀድመን በመለየት ሕክምና እንድታገኝ በማድረግ ማገገሚያዋን በጋራ እንፈልግ በማለት በኢትዮጵያነት ክብርና ፍቅር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡